|
በሀረር ማዘጋጃ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ማስፋፊያ ጽ/ቤት እየተከናወኑ ያሉ ቀጣይ የልማት ስራዎች ሂደት እና ዝግጅት |
|
|
|
Tuesday, 02 March 2010 19:40 |
|
በአሚር ኑር ቀበሌ መስተዳድር (በአው አብዳል መስጊድ አካባቢ) እና በአውሀኪም ቀበሌ መስተዳድር (በአራተኛ አካባቢ)ለሚሰሩት ሁለት የገበያ አዳራሾች የሀረር ማዘጋጃ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ማስፋፊያ ጽ/ቤት በሄራልድ ጋዜጣ የጨረታ ማስታወቂያ በማሳወጅ ተጫራቾችን ከጋበዘ በኋላ የካቲት 29 ቀን2002 ዓ/ም ከጠዋቱ 3፡30የጨረታ ሰነዱ ተጫራቾች እና ታዛቢዎች በተገኙበት ተከፍቷል።
በአሁኑ ወቅት በአውሀኪም ቀበሌ መስተዳድር አካባቢ የሚገነባው የገበያማከል(ማርኬት ሼድ) የጨረታው አሸናፊ ኮንትራክተር ተስፋዬ ፀጋው BC ደረጃ 5 ያሸነፉበት ዋጋ ብር 2.85 ሚሊዮን ሲሆን የግንባታ ስራውን ለመጀመር ቦታውን ተረክበዋል። |